164 ጻድቅ ስለ ሆነው ሕግህ፤በቀን ሰባት ጊዜ አመሰግንሃለሁ።
165 ሕግህን የሚወዱ ብዙ ሰላም አላቸው፤ዕንቅፋትም የለባቸውም።
166 እግዚአብሔር ሆይ፤ ማዳንህን ተስፋ አደርጋለሁ፤ትእዛዝህንም እፈጽማለሁ።
167 ነፍሴ ምስክርነትህን ትጠብቃለች፤እጅግ እወደዋለሁና።
168 መንገዴ ሁሉ በፊትህ ግልጽ ነውና፣ሕግህንና ምስክርነትህን እጠብቃለሁ።
169 እግዚአብሔር ሆይ፤ ጩኸቴ ከፊትህ ይድረስ፤እንደ ቃልህም ማስተዋልን ስጠኝ።
170 ልመናዬ ከፊትህ ይድረስ፤እንደ ቃልህም ታደገኝ።