6 አምላክ ሆይ፤ ስለምትመልስልኝ አንተን እጣራለሁ፤ጆሮህን ወደ እኔ ጣል አድርገህ ጸሎቴን ስማ።
7 ከጠላቶቻቸው መተገኛ ያደረጉህን፣በቀኝ እጅህ የምትታደግ ሆይ፤ጽኑ ፍቅርህን ድንቅ አድርገህ ግለጥ።
8 እንደ ዐይንህ ብሌን ጠብቀኝ፤በክንፎችህም ጥላ ሰውረኝ፤
9 ከሚያስጨንቁኝ ከክፉዎች፣ከሚከብቡኝ አደገኛ ባላንጣዎቼ ጋርደኝ።
10 ደንዳና ልባቸውን ደፈኑት፤በአፋቸውም ትዕቢት ይናገራሉ።
11 አሳደው ደረሱብኝ፤ ከበቡኝም፤መሬት ላይ ሊዘርሩኝም አፈጠጡብኝ።
12 እነርሱ ለንጥቂያ እንደሚጓጓ አንበሳ፣በስውርም እንደሚያደባ ደቦል አንበሳ ናቸው።