19 የጭንቀቴንና የመንከራተቴን፣ምሬትንና ሐሞትን አስባለሁ።
20 ዘወትር አስበዋለሁ፤ነፍሴም በውስጤ ተዋርዳለች።
21 ሆኖም ይህን አስባለሁእንግዲያስ ተስፋ አለኝ፤
22 ያልጠፋነው ከእግዚአብሔር ታላቅ ፍቅር የተነሣ ነው፤ርኅራኄው አያልቅምና።
23 ማለዳ ማለዳ አዲስ ነው፤ታማኝነትህም ብዙ ነው።
24 ራሴን እንዲህ አልሁት፤ “እግዚአብሔር ዕድል ፈንታዬ ነው፤ስለዚህ ተስፋ አደርገዋለሁ።
25 እርሱን ተስፋ ለሚያደርጉት፣ለሚፈልገውም ሰው እግዚአብሔር መልካም ነው።