1 ከመዝሙር ሁሉ የሚበልጥ የሰሎሞን መዝሙር።
2 በከንፈሩ መሳም ይሳመኝፍቅርህ ከወይን ጠጅ ይልቅ ደስ ያሰኛልና።
3 የሽቱህ መዐዛ ደስ ያሰኛል፤ስምህ እንደሚፈስ ሽቱ ነው፤ታዲያ ቈነጃጅት ቢወዱህ ምን ያስደንቃል
4 ይዘኸኝ ሂድ፤ እንፍጠን፤ንጉሡ ወደ ዕልፍኞቹ አምጥቶኛል።በአንተ ደስ ይለናል፤ ሐሤትም እናደርጋለን፤ከወይን ጠጅ ይልቅ ፍቅርህን እንወድሳለን።አንተን እንደዚህ ማፍቀራቸው ትክክል ነው።
5 እናንት የኢየሩሳሌም ቈነጃጅት ሆይ፤እኔ ጥቊር ነኝ፤ ይሁን እንጂ ውብ ነኝ፤ጥቊረቴ እንደ ቄዳር ድንኳኖች፣እንደ ሰሎሞን ቤተ መንግሥት መጋረጃዎችም ነው።
6 ጥቊር ስለ ሆንሁ ትኵር ብላችሁ አትዩኝ፤መልኬን ያጠቈረው ፀሓይ ነውና፤የእናቴ ልጆች ወንድሞቼ ተቈጡኝ፤የወይን ተክል ቦታዎችም ጠባቂ አደረጉኝ፤የራሴን የወይን ተክል ቦታ ተውሁት።