4 አዶ፣ ጌንቶን፣ አብያ፣
5 ሚያሚን፣ መዓድያ፣ ቢልጋ፣
6 ሸማያ፣ ዮያሪብ፣ ዮዳኤ፣
7 ሰሉ፣ ዓሞቅ፣ ኬልቅያስና ዮዳኤ።እነዚህ በኢያሱ ዘመን የካህናቱና የወንድሞቻቸው አለቆች ነበሩ።
8 ሌዋውያኑ ደግሞ ኢያሱ፣ ቢንዊ፣ ቀድምኤል፣ ሰራብያ፣ ይሁዳ እንዲሁም ከወንድሞቹ ጋር የምስጋና መዝሙር ኀላፊ የሆነው መታንያ ነበሩ።
9 ወንድሞቻቸው የሆኑት በቅቡቅያና ዑኒም በአገልግሎት ጊዜ ከእነርሱ ትይዩ ይቆሙ ነበር።
10 ኢያሱ ዮአቂምን ወለደ፤ ዮአቂም ኤልያሴብን ወለደ፤ ኤልያሴብ ዮአዳን ወለደ፤