2 ይህም የጨለማና የጭጋግ ቀን፣የደመናና የድቅድቅ ጨለማ ቀን ነው።የንጋት ብርሃን በተራሮች ላይ እንደሚወጣ፣ኀያልና ብዙ ሰራዊት ይመጣል፤ከጥንት እንዲህ ዐይነት ከቶ አልነበረም፤በሚመጡትም ዘመናት እንዲህ ዐይነት ከቶ አይሆንም።
3 በፊታቸው፣ እሳት ይባላል፤በኋላቸውም ነበልባል ይለበልባል፤በፊታቸው ምድሪቱ እንደ ዔድን ገነት ናት፤በኋላቸውም የሚቀረው ባዶ ምድረ በዳ ነው፤ምንም አያመልጣቸውም።
4 መልካቸው እንደ ፈረስ መልክ ነው፤እንደ ጦር ፈረስም ይጋልባሉ።
5 ገለባ እንደሚበላ እንደሚንጣጣ እሳት፣ለጦርነት እንደ ተዘጋጀ ኀያል ሰራዊት፣የሠረገሎችን ድምፅ የሚመስል ድምፅ እያሰሙ፣በተራሮች ጫፍ ላይ ይዘላሉ።
6 በእነርሱ ፊት ሕዝቦች ይርዳሉ፤የሁሉም ፊት ይገረጣል።
7 እንደ ተዋጊዎች ድንገት አደጋ ይጥላሉ፤እንደ ወታደሮችም ቅጥርን ይዘላሉ፤ከመንገዳቸውም ሳይወጡ፣አቅጣጫ ይዘው ይጓዛሉ።
8 እርስ በርሳቸው አይገፋፉም፤እያንዳንዱ መስመሩን ጠብቆ ይሄዳል፤መስመራቸውን ሳይለቁ፣መከላከያውን ሰብረው ያልፋሉ።