ሆሴዕ 9:6-12 NASV

6 ከጥፋት ቢያመልጡም እንኳ፣ግብፅ ትሰበስባቸዋለች፤ሜምፎስም ትቀብራቸዋለች።የብር ሀብታቸውን ዳዋ ያለብሰዋል፤ድንኳኖቻቸውም እሾኽ ይወርሰዋል።

7 የቅጣት ቀን መጥቶአል፤የፍርድም ቀን ቀርቦአል፤እስራኤልም ይህን ይወቅ!ኀጢአታችሁ ብዙ፣ጠላትነታችሁም ታላቅ ስለ ሆነ፣ነቢዩ እንደ ሞኝ፣መንፈሳዊውም ሰው እንደ እብድ ተቈጥሮአል።

8 ነቢዩ ከአምላኬ ጋር ሆኖ፣የኤፍሬም ጠባቂ ነው፤ዳሩ ግን በመንገዱ ሁሉ ወጥመድ፣በአምላኩም ቤት ጠላትነት ይጠብቀዋል።

9 በጊብዓ እንደ ነበረው፣በርኵሰት ውስጥ ተዘፍቀዋል፤እግዚአብሔር ክፋታቸውን ያስባል፤ስለ ኀጢአታቸውም ይቀጣቸዋል።

10 “እስራኤልን ማግኘቴ፣የወይንን ፍሬ፣ በምድረ በዳ የማግኘት ያህል ነበር፤አባቶቻችሁንም ማየቴ፣የመጀመሪያውን የበለስ ፍሬ የማየት ያህል ነበር፤ወደ ብዔልፌጎር በመጡ ጊዜ ግን፣ለዚያ አሳፋሪ ጣዖት ራሳቸውን ለዩ፤እንደ ወደዱትም ጣዖት የረከሱ ሆኑ።

11 የኤፍሬም ክብር እንደ ወፍ በሮ ይጠፋል፤መውለድ፣ ማርገዝና መፀነስ የለም።

12 ልጆችን ቢያሳድጉ እንኳ፣ልጅ አልባ እስኪሆኑ ድረስ እነጥቃቸዋለሁ፤ፊቴን ከእነርሱ በመለስሁ ጊዜ፣ወዮ ለእነርሱ