ሰቆቃወ 2:1-7 NASV

1 እግዚአብሔር የጽዮንን ሴት ልጅ፣በቍጣው ደመና እንዴት ጋረዳት!ከሰማይ ወደ ምድር፣የእስራኤልን ክብር ወርውሮ ጣለው፤በቍጣው ቀን፣የእግሩን መቀመጫ አላስታወሰም።

2 የያዕቆብን መኖሪያ ሁሉ፣እግዚአብሔር ያለ ርኅራኄ ዋጣቸው፤የይሁዳን ሴት ልጅ ምሽጎች፣በቍጣው አፈረሳቸው፤መንግሥቷንና መሳፍንቷን፣በማዋረድ ወደ ምድር ጣላቸው።

3 በጽኑ ቍጣው፣የእስራኤልን ቀንድ ሁሉ ሰበረ፤ጠላት በተቃረበ ጊዜ፣ቀኝ እጁን ወደ ኋላ መለሰ፤በዙሪያው ያለውን ሁሉ እንደሚበላ እሳት፣በያዕቆብ ላይ የእሳት ነበልባል ነደደ።

4 እንደ ጠላት ቀስቱን ገተረ፤ቀኝ እጁ ተዘጋጅታለች፤ለዐይን ደስ የሚያሰኙትን ሁሉ፤እንደ ጠላት ዐረዳቸው፤በጽዮን ሴት ልጅ ድንኳን ላይ፣ቍጣውን እንደ እሳት አፈሰሰ።

5 እግዚአብሔር እንደ ጠላት ሆነ፤እስራኤልንም ዋጠ፤ቤተ መንግሥቶቿን ሁሉ ዋጠ፤ምሽጎቿን አፈራረሰ፤በይሁዳ ሴት ልጅ፣ለቅሶንና ሰቈቃን አበዛ።

6 ማደሪያውን እንደ አትክልት ስፍራ ባዶ አደረገ፤መሰብሰቢያ ስፍራውን አፈረሰ፤ እግዚአብሔር ጽዮንን፣ዓመት በዓላቶቿንና ሰንበታቷን እንድትረሳ አደረጋት፤በጽኑ ቍጣው፣ንጉሡንና ካህኑን እጅግ ናቀ።

7 እግዚአብሔር መሠዊያውን ናቀ፤መቅደሱንም ተወ፤የቤተ መንግሥቶቿን ቅጥሮች፣ለጠላት አሳልፎ ሰጠ፤በዓመት በዓል ቀን እንደሚደረገው በእግዚአብሔር ቤት በኀይል ጮኹ።