ኢዩኤል 2:9-15 NASV

9 ከተማዪቱን ይወራሉ፤በቅጥሩም ላይ ይዘላሉ፤በቤቶች ላይ ዘለው ይወጣሉ፤እንደ ሌባም በመስኮት ይገባሉ።

10 ምድር በፊታቸው ትንቀጠቀጣለች፤ሰማይም ይናወጣል፤ፀሓይና ጨረቃ ይጨልማሉ፤ከዋክብትም ከእንግዲህ ወዲያ አያበሩም።

11 በሰራዊቱ ፊት፣ እግዚአብሔር ያንጐደጒዳል፤የሰራዊቱ ብዛት ስፍር ቊጥር የለውም፤ትእዛዙንም የሚያደርግ እርሱ ኀያል ነው፤ የእግዚአብሔር ቀን ታላቅ፣እጅግም የሚያስፈራ ነው፤ማንስ ሊቋቋመው ይችላል?

12 “አሁንም ቢሆን፣በጾም፣ በልቅሶና በሐዘን፣በፍጹም ልባችሁ ወደ እኔ ተመለሱ” ይላል እግዚአብሔር።

13 ልባችሁን እንጂ፣ልብሳችሁን አትቅደዱ፤ወደ አምላካችሁ ወደ እግዚአብሔር ተመለሱ፤እርሱ መሓሪና ርኅሩኅ፣ቊጣው የዘገየና ፍቅሩ የበዛ፣ክፉ ነገር ከማምጣትም የሚታገሥ ነውና።

14 በምሕረቱ ተመልሶ፣ለአምላካችሁ ለእግዚአብሔር የሚሆነውን፣የእህል ቊርባንና የመጠጥ ቊርባን እንዲተርፋችሁ፣በረከቱን ይሰጣችሁ እንደሆነ ማን ያውቃል?

15 በጽዮን መለከትን ንፉ፤ቅዱስ ጾምን ዐውጁ፤የተቀደሰን ጉባኤ ጥሩ።