1 የእስራኤል የበኵር ልጅ የሮቤል ልጆች፤ ሮቤል የበኵር ልጅ ቢሆንም፣ የአባቱን መኝታ ስላረከሰ፣ የብኵርና መብቱ ለእስራኤል ልጅ ለዮሴፍ ልጆች ተሰጥቶአል። ከዚህም የተነሣ ትውልዱ የበኵርነቱን ተራ ይዞ ሊቈጠር አልቻለም።
2 ይሁዳ ከወንድሞቹ ይልቅ ብርቱ ነበረ፤ ገዥ የወጣው ከእርሱ ቢሆንም፣ የብኵርና መብቱ የተላለፈው ለዮሴፍ ነበረ።
3 የእስራኤል የበኵር ልጅ የሮቤል ወንዶች ልጆች፤ሄኖኅ፣ ፋሉሶ፣ አስሮን፣ ከርሚ።
4 የኢዩኤል ዘሮችልጁ ሸማያ፣ ልጁ ጎግ፣ ልጁሰሜኢ፣