1 የሞቱ ዝንቦች ሽቶን እንደሚያገሙ፣ትንሽ ሞኝነትም ጥበብንና ክብርን ያቀላል።
2 የጠቢብ ልብ ወደ ቀኝ፣የሞኝ ልብ ግን ወደ ግራ ያዘነብላል።
3 ሞኝ በጐዳና ሲሄድ ማስተዋል ይጐድለዋል፤ጅል መሆኑንም ለማንም ይገልጻል።
4 የገዥ ቊጣ በተነሣብህ ጊዜ፣ስፍራህን አትልቀቅ፤ትዕግሥት ታላቁን ጥፋት ጸጥ ያደርጋልና።