4 ለማልቀስ ጊዜ አለው፤ ለመሣቅም ጊዜ አለው፤ለሐዘን ጊዜ አለው፤ ለጭፈራም ጊዜ አለው፤
5 ድንጋይ ለመጣል ጊዜ አለው፤ ድንጋይ ለመሰብሰብም ጊዜ አለው፤ለመተቃቀፍ ጊዜ አለው፤ ለመለያየትም ጊዜ አለው፤
6 ለመፈለግ ጊዜ አለው፤ ለመተው ጊዜ አለው፤ለማስቀመጥ ጊዜ አለው፤ አውጥቶ ለመጣልም ጊዜ አለው፤
7 ለመቅደድ ጊዜ አለው፤ ለመስፋትም ጊዜ አለው፤ለዝምታ ጊዜ አለው፤ ለመናገርም ጊዜ አለው፤
8 ለመውደድ ጊዜ አለው፤ ለመጥላትም ጊዜ አለው፤ለጦርነት ጊዜ አለው፤ ለሰላምም ጊዜ አለው።
9 ሠራተኛ ከጥረቱ የሚያገኘው ትርፍ ምንድን ነው?
10 ሰዎች ይደክሙበት ዘንድ እግዚአብሔር የሰጣቸውን ከባድ የሥራ ጫና አየሁ።