3 የሕዝቤን ሥጋ በላችሁ፤ቈዳቸውን ገፈፋችሁ፤ዐጥንቶቻቸውንም ሰባበራችሁ፤በመጥበሻ እንደሚጠበስ፣በድስት እንደሚቀቀል ሥጋ ቈራረጣችኋቸው።
4 እነርሱም ወደ እግዚአብሔር ይጮኻሉ፤እርሱ ግን አይመልስላቸውም፤ካደረጉት ክፋት የተነሣ፣በዚያ ጊዜ ፊቱን ከእነርሱ ይሰውራል።
5 እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“ሕዝቤን የሚያስቱ ነቢያት፣ሰው ሲያበላቸው፣ ‘ሰላም አለ’ ይላሉ፤ሳያበላቸው ሲቀር ግን፣ጦርነት ሊያውጁበት ይነሣሉ።
6 ስለዚህ ሌሊቱ ያለ ራእይ፣ጨለማውም ያለ ንግርት ይመጣባችኋል፤በነቢያት ላይ ፀሐይ ትጠልቅባቸዋለች፤ቀኑም ይጨልምባቸዋል።
7 ባለ ራእዮች ያፍራሉ፤ንግርተኞችም ይዋረዳሉ፤ሁሉም ፊታቸውን ይሸፍናሉ፤ከእግዚአብሔር መልስ የለምና።”
8 እኔ ግን፣ለያዕቆብ በደሉን፣ለእስራኤልም ኀጢአቱን እነግር ዘንድኀይልን፣ በእግዚአብሔር መንፈስ፣ፍትሕና ብርታት ተሞልቻለሁ።
9 እናንት የያዕቆብ ቤት መሪዎች፣እናንት የእስራኤል ቤት ገዦች፣ፍትሕን የምትንቁ፤ትክክለኛ የሆነውንም ነገር ሁሉ የምታጣምሙ፤ ስሙ፤