ሶፎንያስ 3:2-8 NASV

2 እርሷ ለማንም አትታዘዝም፤የማንንም ዕርምት አትቀበልም፤ በእግዚአብሔር አትታመንም፤ወደ አምላኳም አትቀርብም።

3 ሹሞቿ የሚያገሡ አንበሶች፣ገዦቿ ለነገ የማይሉ፣የምሽት ተኵላዎች ናቸው።

4 ነቢያቷ ትዕቢተኞች፣አታላዮችም ናቸው፤ካህናቷ መቅደሱን ያረክሳሉ፣በሕግም ላይ ያምፃሉ።

5 በእርሷ ውስጥ ያለው እግዚአብሔር ጻድቅ ነው፤ፈጽሞ አይሳሳትም፤በየማለዳው ቅን ፍርድ ይሰጣል፤በየቀኑም አይደክምም፤ዐመፀኞች ግን ዕፍረት አያውቁም።

6 “ሕዝቦችን አጥፍቻለሁ፤ምሽጋቸው ተደምስሶአል፤ማንም እንዳያልፍባቸው፣መንገዳቸውን ባድማ አደረግሁ፤ከተሞቻቸው ተደምስሰዋል፤አንድም ሰው የለም፤ ነዋሪም ከቶ አይገኝባቸውም።

7 እኔም ከተማዪቱን፣‘በእርግጥ ትፈሪኛለሽ፤ዕርምትም ትቀበያለሽ’ አልኋት፤ስለዚህ መኖሪያዋ አይጠፋም፤ቅጣቴም ሁሉ በእርሷ ላይ አይደርስም።እነርሱ ግን በሚያደርጉት ሁሉ፣ክፋትንም በመፈጸም እየተጉ ሄዱ።

8 እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“ስለዚህ እስከምፈርድበት ቀን ድረስጠብቁኝ፤አሕዛብን ላከማች፣መንግሥታትን ልሰበስብ፣መዓቴንና ጽኑ ቊጣዬን፣በላያቸው ላፈስ ወስኛለሁ፤በቅናቴ ቍጣ እሳት፣መላዋ ምድር ትቃጠላለችና።