ሶፎንያስ
ምዕራፎች 2
መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም
1እናንት ዕረፍት የሌላችሁ ሕዝብ ሆይ፤በአንድነት ተሰብሰቡ፤ ተከማቹም፤
2የተወሰነው ጊዜ ሳይደርስ፣ቀኑ እንደ ገለባ ሳይጠራርጋችሁ፣ የእግዚአብሔር ጽኑ ቊጣ በእናንተ ላይ ሳይመጣ፣ የእግዚአብሔር የመዓት ቀንሳይደርስባችሁ ተሰብሰቡ።
3እናንት የምድር ትሑታን ሁሉ፣ትእዛዙን የምትፈጽሙ፣ እግዚአብሔርን እሹ፤ጽድቅንና ትሕትናን ፈልጉ፤ በእግዚአብሔር የቊጣ ቀን፣ትሰወሩ ይሆናል።