12 ለሰዎች፣ በሕይወት እያሉ ደስ ከመሰኘትና መልካምን ነገር ከማድረግ የተሻለ ነገር እንደሌለ ዐወቅሁ።
13 ሰው ሁሉ ይበላና ይጠጣ ዘንድ፣ በሚደክምበትም ሁሉ ርካታን ያገኝ ዘንድ ይህ የእግዚአብሔር ችሮታ ነው።
14 እግዚአብሔር ያደረገው ሁሉ ለዘላለም እንደሚኖር ዐውቃለሁ፤ በእርሱ ላይ ምንም አይጨመርም፤ ከእርሱም ምንም አይቀነስም፤ ሰዎች ያከብሩት ዘንድ ይህን አደረገ።
15 አሁን ያለው ከዚህ በፊት የነበረው ነው፤ወደ ፊት የሚሆነውም ቀድሞ የነበረ ነው፤እግዚአብሔርም ያለፈውን መልሶ ይሻዋል።
16 ከፀሓይ በታችም ሌላ ነገር አየሁ፤በፍርድ ቦታ ዐመፅ ነበር፤በፍትሕ ቦታ ግፍ ነበር።
17 እኔም በልቤ“ለማንኛውም ድርጊት፣ለማንኛውም ተግባር ጊዜ ስላለው፣እግዚአብሔር ጻድቁንና ኀጢአተኛውን ወደ ፍርድ ያመጣቸዋል”ብዬ አሰብሁ።
18 እንዲህም ብዬ አሰብሁ፤ “ሰዎች፣ እንደ እንስሳት መሆናቸውን ያዩ ዘንድ እግዚአብሔር ይፈትናቸዋል።