5 ድንጋይ ለመጣል ጊዜ አለው፤ ድንጋይ ለመሰብሰብም ጊዜ አለው፤ለመተቃቀፍ ጊዜ አለው፤ ለመለያየትም ጊዜ አለው፤
6 ለመፈለግ ጊዜ አለው፤ ለመተው ጊዜ አለው፤ለማስቀመጥ ጊዜ አለው፤ አውጥቶ ለመጣልም ጊዜ አለው፤
7 ለመቅደድ ጊዜ አለው፤ ለመስፋትም ጊዜ አለው፤ለዝምታ ጊዜ አለው፤ ለመናገርም ጊዜ አለው፤
8 ለመውደድ ጊዜ አለው፤ ለመጥላትም ጊዜ አለው፤ለጦርነት ጊዜ አለው፤ ለሰላምም ጊዜ አለው።
9 ሠራተኛ ከጥረቱ የሚያገኘው ትርፍ ምንድን ነው?
10 ሰዎች ይደክሙበት ዘንድ እግዚአብሔር የሰጣቸውን ከባድ የሥራ ጫና አየሁ።
11 ሁሉንም ነገር በጊዜው ውብ አድርጎ ሠራው፤ በሰዎችም ልብ ዘላለማዊነትን አኖረ፤ ይሁን እንጂ እግዚአብሔር ከመጀመሪያ እስከ መጨረሻ ያደረገውን ማወቅ አይችሉም።