1 ሮብዓም መንግሥቱን ከመሠረተና ካጸና በኋላ እርሱና እስራኤል ሁሉ የእግዚአብሔርን ሕግ ተዉ።
2 እግዚአብሔርን ከመበደላቸው የተነሣም፣ ሮብዓም በነገሠ በአምስተኛው ዓመት የግብፅ ንጉሥ ሺሻቅ በኢየሩሳሌም ላይ ዘመተ።
3 ከግብፅ አብረውት የመጡትን ዐሥራ ሁለት ሺህ ሠረገላዎች፣ ስድሳ ሺ ፈረሰኞችና ስፍር ቊጥር የሌላቸውን የሊብያ፣ የሱኪምና የኢትዮጵያ ወታደሮችን ይዞ፣
4 የተመሸጉትን የይሁዳ ከተሞች በቁጥጥሩ ሥር በማድረግ እስከ ኢየሩሳሌም ዘለቀ።