ሚክያስ 2:1-7 NASV

1 ክፉ ለመሥራት ለሚያቅዱ፣በመኝታቸው ሳሉ ተንኰል ለሚያውጠነጥኑ ወዮላቸው!ሲነጋ በማለዳ ይፈጽሙታል፤የሚያደርጉበት ኀይል በእጃቸው ነውና።

2 ዕርሻ ይመኛሉ፤ ይይዙታልም፤ቤት ይመኛሉ፤ ይወስዱታልም፤የሰውን ቤት፣የባልንጀራን ርስት አታልለው ይወስዳሉ።

3 ስለዚህ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“እነሆ፤ በዚያ ሕዝብ ላይ ጥፋት ላመጣ ዐቅጃለሁ፤ከዚህም ለማምለጥ አትችሉም።ከእንግዲህ በትዕቢት አትመላለሱም፤የመከራ ጊዜ ይሆናልና።

4 በዚያ ቀን ሰዎች ይሣለቁባችኋል፤በሐዘን እንጒርጒሮ እንዲህ እያሉ ያፌዙባችኋል፤‘እኛ ፈጽሞ ጠፍተናል፤የወገኔ ርስት ተከፋፍሎአል።ከእኔ ነጥቆ ወስዶ፣ዕርሻዎቻችንን ላሸነፉን አከፋፈለ።’

5 ስለዚህ በእግዚአብሔር ጉባኤ ውስጥ፣መሬት በዕጣ የሚያካፍል ማንም አይኖርም።

6 ነቢያቶቻቸው፣ “ትንቢት አትናገርብን፤ስለ እነዚህ ነገሮች ትንቢት አትናገር፤ውርደት አይደርስብንም” ይላሉ።

7 የያዕቆብ ቤት ሆይ፤ እንዲህ ሊባል ይገባልን?“የእግዚአብሔር መንፈስ የማይታገሥ ነውን?እንዲህ ያሉት ነገሮችንስ ያደርጋልን?”“መንገዱ ቀና ለሆነ፣ቃሌ መልካም አያደርግምን?