ዘዳግም 33:15-21 NASV

15 ከጥንት ተራሮች በተገኘ ምርጥ ስጦታ፣በዘላለማዊ ኰረብቶች ፍሬያማነት፤

16 ምድር በምታስገኘው ምርጥ ስጦታና በሙላቷ፣በሚቃጠለው ቊጥቋጦም ውስጥ በነበረው በእርሱ ሞገስ።እነዚህ ሁሉ በወንድሞቹ መካከል ገዥ በሆነው፣በዮሴፍ ዐናት ላይ ይውረዱ።

17 በግርማው እንደ በኵር ኰርማ ነው፤ቀንዶቹም የጐሽ ቀንዶች ናቸው።በእነርሱም ሕዝቦችን፣በምድር ዳርቻ ላይ ያሉትን እንኳ ሳይቀር ይወጋል፤እነርሱም የኤፍሬም ዐሥር ሺዎቹ ናቸው፤የምናሴም ሺዎቹ እንደዚሁ ናቸው።”

18 ስለ ዛብሎንም እንዲህ አለ፦“ዛብሎን ሆይ፤ ወደ ውጭ በመውጣትህ፣አንተም ይሳኮር በድንኳኖችህ ውስጥ ደስ ይበልህ፤

19 አሕዛብን ወደ ተራራው ይጠራሉ፤በዚያም የጽድቅን መሥዋዕት ያቀርባሉ።በባሕሮች ውስጥ ያለውን በተትረፈረፈ ብልጽግና፣በአሸዋውም ውስጥ የተደበቀውን ሀብት ይደሰቱበታል።”

20 ስለ ጋድም እንዲህ አለ፦“የጋድን ግዛት የሚያሰፋ የተመሰገነ ነው!ክንድንና ራስን በመገነጣጠል፣ጋድ እንደ አንበሳ በዚያ ይኖራል።

21 ለም የሆነውን መሬት ለራሱ መረጠ፤የአለቃም ድርሻ ለእርሱ ተጠብቆለታል።የሕዝቡ መሪዎች በተሰበሰቡ ጊዜ፣ የእግዚአብሔርን (ያህዌ) የቅን ፈቃድና፣በእስራኤል ላይ የበየነውን ፍርዱን ፈጸመ።”