5 ሐሰተኛ ምስክር ከቅጣት አያመልጥም፤ውሸት የሚነዛም ሳይቀጣ አይቀርም።
6 ብዙ ሰዎች በገዥ ዘንድ ሞገስ ለማግኘት ያሸረግዳሉ፤ስጦታን ከሚሰጥ ሰው ጋር ሁሉም ወዳጅ ነው።
7 ድኻ በሥጋ ዘመዶቹ ሁሉ የተጠላ ነው፤ታዲያ ወዳጆቹማ የቱን ያህል ይሸሹት!እየተከታተለ ቢለማመጣቸውም፣ከቶ አያገኛቸውም።
8 ጥበብን ገንዘቡ የሚያደርጋት ነፍሱን ይወዳል፤ማስተዋልን የሚወዳት ይሳካለታል።
9 ሐሰተኛ ምስክር ከቅጣት አያመልጥም፤ውሸት የሚነዛም ይጠፋል።
10 ተላላ ተንደላቆ መኖር አይገባውም፤ባሪያ የመሳፍንት ገዥ ከሆነማ የቱን ያህል ይከፋ!
11 ጥበብ ሰውን ታጋሽ ታደርገዋለች፤በደልን ንቆ መተውም መከበሪያው ነው።