27 ማድረግ እየቻልህለሚገባቸው መልካም ነገር ከማድረግ አትቈጠብ።
28 አሁን በእጅህ እያለ፣ጎረቤትህን፣ “ቈይተህ ተመለስ፤ ነገ እሰጥሃለሁ” አትበለው።
29 አንተን ተማምኖ በአጠገብህ በተቀመጠ፣በጎረቤትህ ላይ ክፉ አትምከርበት።
30 ምንም ጒዳት ሳያደርስብህ፣ያለ ምክንያት ሰውን አትክሰስ።
31 በክፉ ሰው አትቅና፤የትኛውንም መንገዱን አትምረጥ፤
32 እግዚአብሔር ጠማማን ሁሉ ይጸየፋልና፤ለቅን ሰው ግን ምስጢሩን ይገልጥለታል።
33 የእግዚአብሔር ርግማን በክፉዎች ቤት ላይ ነው፤የጻድቃንን ቤት ግን ይባርካል።