15 ስለዚህ በቅጽበት መዓት ይወርድበታል፤በድንገት ይጠፋል፤ መዳኛም የለውም።
16 እግዚአብሔር የሚጠላቸው ስድስት ነገሮች አሉ፤የሚጸየፋቸውም ሰባት ናቸው፤ እነርሱም፦
17 ትዕቢተኛ ዐይን፣ሐሰተኛ ምላስ፣ንጹሕ ደም የሚያፈሱ እጆች፣
18 ክፋትን የሚያውጠነጥን ልብ፣ወደ ክፋት የሚቻኰሉ እግሮች፣
19 በውሸት ላይ ውሸት የሚጨምር ሐሰተኛ ምስክር፣በወንድማማቾች መካከል ጠብን የሚጭር ሰው።
20 ልጄ ሆይ፤ የአባትህን ትእዛዝ አክብር፤የእናትህንም ትምህርት አትተው።
21 ምንጊዜም በልብህ አኑራቸው፤በዐንገትህም ዙሪያ እሰራቸው።