1 ሁለተኛው ዕጣ ለስምዖን ነገድ በየጐሣ በየጐሣው ወጣ፤ ርስታቸውም ዙሪያውን በይሁዳ ነገድ ርስት የተከበበ ነበር፤
2 ይህም የሚከተሉትን ያካትታል፤ ቤርሳቤህ፣ ሤባ፣ ሞላዳ፣
3 ሐጸር ሹዓል፣ ባላ፣ ዔጼም፣
4 ኤልቶላድ፣ በቱል፣ ሔርማ፣
5 ጺቅላግ፣ ቤትማርካቦት፣ ሐጸርሱሳ፣
6 ቤተለባኦትና ሻሩሔን ነበሩ፤ እነዚህ ዐሥራ ሦስት ከተሞችና መንደሮቻቸው ናቸው።
7 ዓይን፣ ሪሞን፣ ዔቴርና ዓሻን የተባሉት አራት ከተሞቻቸውና መንደሮቻቸው፣