17 ለድኻ የሚራራ ለእግዚአብሔር ያበድራል፤ስላደረገውም ተግባር ዋጋ ይከፍለዋል።
18 ገና ተስፋ ሳለ፣ ልጅህን ሥርዐት አስይዘው፤ሲሞት ዝም ብለህ አትየው።
19 ግልፍተኛ ሰው ቅጣትን መቀበል ይገባዋል፤በምሕረት ካለፍኸው ሌላም ጊዜ አይቀርልህም።
20 ምክርን ስማ፤ ተግሣጽን ተቀበል፤በመጨረሻም ጠቢብ ትሆናለህ።
21 በሰው ልብ ብዙ ሐሳብ አለ፤የሚፈጸመው ግን የእግዚአብሔር ሐሳብ ነው።
22 ሰው የሚመኘው ጽኑ ፍቅር ነው፤ውሸታም ከመሆንም ድኻ መሆን ይሻላል።
23 እግዚአብሔርን መፍራት ወደ ሕይወት ይመራል፤እንዲህ ያለውም ሰው እፎይ ብሎ ያርፋል፤ መከራም አያገኘውም።