1 በክፉ ሰዎች አትቅና፤ጓደኝነታቸውም አይመርህ፤
2 ልባቸው ዐመፅን ያውጠነጥናልና፤ከንፈራቸውም ሸፍጥ ያወራል።
3 ቤት በጥበብ ይሠራል፤በማስተዋልም ይጸናል፤
4 በዕውቀትም ውድና ውብ በሆነ ንብረት፣ክፍሎቹ ይሞላሉ።
5 ጠቢብ ሰው ታላቅ ኀይል አለው፤ዕውቀት ያለውም ሰው ብርታትን ይጨምራል፤
6 ጦርነት ለመግጠም መልካም ምክር፣ድል ለማድረግም ብዙ አማካሪዎች ያስፈልጋሉ።