3 የአመንዝራ ሴት ከንፈር ማር ያንጠባጥባልና፤አንደበቷም ከቅቤ ይለሰልሳል፤
4 በመጨረሻ ግን እንደ እሬት ትመራለች፤ሁለት አፍ እንዳለውም ስል ሰይፍ ትሆናለች።
5 እግሮቿ ወደ ሞት ይወርዳሉ፤ርምጃዎቿም በቀጥታ ወደ ሲኦል ያመራሉ።
6 ስለ ሕይወት መንገድ ደንታ የላትም፤መንገዶቿ ዘወርዋራ ናቸው፤ ለእርሷ ግን አይታወቃትም።
7 እንግዲህ፣ ልጆቼ ሆይ፤ አድምጡኝ፤ከምነግራችሁ ቃል ፈቀቅ አትበሉ።
8 መንገድህን ከእርሷ አርቅ፤በደጃፏም አትለፍ፤
9 ይኸውም ጒብዝናህን ለሌሎች፣ዕድሜህንም ለጨካኞች እንዳትሰጥ ነው፤