ዘካርያስ 9:7-13 NASV

7 ደሙን ከአፋቸው፣የተከለከለውንም ምግብ ከመንጋጋቸው አወጣለሁ።የተረፉት ለአምላካችን ይሆናሉ፤በይሁዳም አለቆች ይሆናሉ፤አቃሮንም እንደ ኢያቡሳዊ ይሆናል።

8 እኔ ግን ቤቴንከዘራፊ ኀይሎች እጠብቃለሁ፤ጨቋኝ ከእንግዲህ ሕዝቤን አይወርስም፤አሁን ነቅቼ እጠብቃለሁና።

9 አንቺ የጽዮን ልጅ ሆይ፤ እጅግ ደስ ይበልሽ፤አንቺ የኢየሩሳሌም ልጅ ሆይ፤ እልል በዪ፤እነሆ፤ ጻድቁና አዳኙ ንጉሥሽ፣ትሑት ሆኖ፣ በአህያ ላይ ተቀምጦ፣በአህያ ግልገል፣ በውርንጫዪቱ ላይ ሆኖወደ አንቺ ይመጣል።

10 ሠረገሎችን ከኤፍሬም፣የጦር ፈረሶችን ከኢየሩሳሌም እወስዳለሁ፤የጦርነቱም ቀስት ይሰበራል፤ሰላምን ለአሕዛብ ያውጃል፤ግዛቱም ከባሕር እስከ ባሕር፣ከወንዙም እስከ ምድር ዳር ድረስ ይዘረጋል።

11 ለአንቺ ደግሞ፣ ከአንቺ ጋር ከገባሁት የደም ቃል ኪዳን የተነሣ፣እስረኞችሽን ውሃ ከሌለበት ጒድጓድ ነጻ እለቃቸዋለሁ።

12 እናንት በተስፋ የምትኖሩ እስረኞች፤ ወደ ምሽጎቻችሁ ተመለሱ፤አሁንም ቢሆን ሁለት ዕጥፍ አድርጌ እንደምመልስላችሁ እናገራለሁ።

13 ቀስቴን እንደ ገተርሁ፣ ይሁዳን እገትረዋለሁ፤ኤፍሬምንም ፍላጻ አደርገዋለሁ፤ጽዮን ሆይ፤ ልጆችሽን አስነሣለሁ፤ግሪክ ሆይ፤ በአንቺ ልጆች ላይ ይነሣሉ፤እንደ ተዋጊ ሰይፍም አደርግሻለሁ።