4 በዚያን ጊዜ ሞገስንና መልካም ስምን፣በእግዚአብሔርና በሰው ዘንድ ታገኛለህ።
5 በፍጹም ልብህ በእግዚአብሔር ታመን፤በራስህ ማስተዋል አትደገፍ፤
6 በመንገድህ ሁሉ እርሱን ዕወቅ፤እርሱም ጐዳናህን ቀና ያደርገዋል።
7 በራስህ አስተያየት ጠቢብ ነኝ አትበል፤ እግዚአብሔርን ፍራ፤ ከክፉም ራቅ።
8 ይህም ለሰውነትህ ጤንነትን፣ለዐጥንትህም ልምላሜን ያመጣልሃል።
9 እግዚአብሔርን በሀብትህ፣ከምርትህ ሁሉ በኵራት አክብረው፤
10 ይህን ብታደርግ፣ ጎተራህ ሞልቶ ይትረፈረፋል፤መጥመቂያህም በአዲስ የወይን ጠጅ ቲፍ ብሎ ይሞላል።