44 እነሆ፤ የሰላምታሽ ድምፅ ጆሮዬ እንደ ገባ፣ በማሕፀኔ ያለው ፅንስ በደስታ ዘሎአልና።
45 ጌታ ይፈጸማል ብሎ የነገራትን ያመነች እርሷ የተባረከች ናት!”
46 ማርያምም እንዲህ አለች፤“ነፍሴ ጌታን ከፍ ከፍ ታደርገዋለች፤
47 መንፈሴም በመድኀኒቴ በእግዚአብሔር ደስ ትሰኛለች፤
48 እርሱ የባሪያውን መዋረድ ተመልክቶአልና።ከዛሬ ጀምሮ ትውልድ ሁሉብፅዕት ይሉኛል፤
49 ኀያል የሆነው እርሱ ታላቅነገር አድርጎልኛልና፤ ስሙም ቅዱስ ነው፤
50 ምሕረቱም ለሚፈሩት ከትውልድእስከ ትውልድ ይኖራል።