70 ይህም ጥንት በቅዱሳን ነቢያቱ አፍ እንደ ተናገረው፣
71 ማዳኑም ከጠላቶቻችንና፣ከተፃራሪዎቻችን ሁሉ እጅ ነው፤
72 ይህንም ያደረገው ለአባቶቻችን ምሕረቱን ለማሳየት፣ቅዱስ ኪዳኑን ለማስታወስ፣
73 ለአባታችን ለአብርሃም የማለውን መሐላ ለማሰብ፣
74 ከጠላቶቻችን እጅ አውጥቶ፣ያለ ፍርሀት እንድናገለግለው፣
75 በዘመናችንም ሁሉ በቅድስናና በጽድቅ በፊቱ ሊያቆመን ነው።
76 ደግሞም አንተ ሕፃን ሆይ፤ የልዑል ነቢይ ትባላለህ፤የጌታን መንገድ ለማዘጋጀት በፊቱ ትሄዳለህና፤