1 “ከሴት የተወለደ ሰው፣ዘመኑ አጭርና በመከራ የተሞላ ነው፤
2 እንደ አበባ ይፈካል፤ ይረግፋልም፤እንደ ጥላ ይፈጥናል፤ አይጸናምም።
3 እንደዚህ ባለ ሰው ላይ ዐይንህን ታሳርፋለህን?ለፍርድስ በፊትህ ታቀርበዋለህን?
4 ከርኩስ ነገር ውስጥ ንጹሕን ማን ሊያወጣ ይችላል?አንድ እንኳ የሚችል የለም!