ኢዮብ

ምዕራፎች 35

መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም

1ኤሊሁ ንግግሩን በመቀጠል እንዲህ አለ፤ 2“ ‘በእግዚአብሔር ፊት ንጹሕ ነኝ’ ማለትህ፣ትክክል ይመስልሃልን? 3ደግሞ ‘ያገኘሁት ጥቅም ምንድን ነው?ኀጢአት ባለ መሥራቴስ ምን አተረፍሁ?’ ብለህ ጠይቀኸዋል። 4“ለአንተና አብረውህ ላሉት ባልንጀሮችህ፣መልስ መስጠት እፈልጋለሁ። 5ቀና ብለህ ወደ ሰማይ እይ፤ከአንተ በላይ ከፍ ብለው ያሉትንም ደመናት ተመልከት። 6ኀጢአትህስ ቢበዛ እርሱን ምን ትጐዳዋለህ?ኀጢአትህስ ቢበዛ ምን ያደርገዋል? 7ጻድቅ ብትሆንም ለእርሱ ምን ትሰጠዋለህ?ከእጅህስ ምን ይቀበላል? 8ክፋትህ የሚጐዳው እንዳንተ ያለውን ሰው ብቻ ነው፤ጽድቅህም የሚጠቅመው የሰውን ልጆች ብቻ ነው። 9“ሰው ከጭቈና ብዛት የተነሣ ይጮኻል፤ከኀያሉም ክንድ ሥር ለመውጣት ለርዳታ ይጣራል። 10ነገር ግን እንዲህ የሚል የለም፤ ‘ፈጣሪዬ እግዚአብሔር ወዴት ነው?በሌሊት መዝሙርን የሚሰጥ፣ 11ከምድር እንስሳት ይልቅ የሚያስተምረን፣ከሰማይ ወፎችም ይልቅ ጠቢባን የሚያደርገን፣ እርሱ የት አለ?’ 12ከዐመፀኞች ትዕቢት የተነሣ፣ሰዎች ሲጮኹ አይመልስላቸውም፤ 13በእርግጥ እግዚአብሔር ከንቱ ጩኸታቸውን አይሰማም፤ሁሉን የሚችል አምላክ አያዳምጣቸውም። 14ጒዳይህን ፊቱ አቅርበህ፣ብዙ ጠብቀኸው፣ግን እንዳላየኸው ስትናገር፣ታዲያ፣ አንተን እንዴት ይስማህ! 15ደግሞም፣ ቍጣው ቅጣት እንደማያስከትል፣ኀጢአትንም ከቍጥር እንደማያስገባ ተናግረሃል። 16ስለዚህ ኢዮብ አፉን በከንቱ ይከፍታል፤ዕውቀት አልባ ቃላትም ያበዛል።”