4 አንተ በቍጣ የነደድህ እንደሆነ፣ምድር ባዶዋን ትቀራለች?ወይስ ዐለት ከሥፍራው ተነቅሎ ይወሰዳል?
5 “የክፉዎች መብራት ይጠፋል፤የእሳቱም ነበልባል ድርግም ይላል።
6 የድንኳኑ ብርሃን ይጨልማል፤መብራቱም በላዩ ይጠፋል፤
7 የርምጃው ብርታት ይደክማል፤የገዛ ዕቅዱም ይጥለዋል።
8 እግሩ በወጥመድ ይያዛል፤በመረብም ይተበተባል።
9 አሽክላ ተረከዙን ይይዘዋል፤ወስፈንጥርም ያጣብቀዋል።
10 በምድር ላይ የሸምበቆ ገመድ፣በመንገዱም ላይ ወጥመድ በስውር ይቀመጥለታል።