1 ኢዮብም እንዲህ ሲል መለሰ፤
2 “ኀይል የሌለውን ምንኛ ረዳኸው!ደካማውንስ ምንኛ አዳንኸው!
3 ጥበብ የሌለውን ምንኛ መከርኸው!ታላቅ ዕውቀትንስ ምንኛ ገለጥህለት!
4 ይህን ቃል እንድትናገር የረዳህ ማን ነው?የማንስ መንፈስ በአንደበትህ ተጠቀመ?