16 ለችግረኛው አባት፣ለባይተዋሩ ተሟጋች ነበርሁ።
17 የኀጢአተኛውን ክራንቻ ሰበርሁ፤የነጠቀውንም ከጥርሶቹ አስጣልሁ።
18 “እኔም በልቤ እንዲህ አልሁ፤ ‘ዘመኔ እንደ አሸዋ በዝቶ፣በቤቴ ተደላድዬ እሞታለሁ፤
19 ሥሬ ወደ ውሃ ይዘረጋል፤ጠልም በቅርንጫፌ ላይ ያድራል፤
20 ክብሬ በውስጤ አዲስ እንደሆነ፣ቀስትም በእጄ እንደ በረታ ይኖራል።’
21 “ሰዎች ምክሬን በጸጥታ በመጠባበቅ፣በጒጒት አዳመጡኝ።
22 እኔ ከተናገርሁ በኋላ፣ የሚናገር ሰው አልነበረም፤ቃሌም እየተንጠባጠበ በጆሯቸው ይገባ ነበር።