2 “እናንት ጠቢባን፣ ቃሌን ስሙ፤ዐዋቂዎችም አድምጡኝ።
3 ምላስ ምግብን አጣጥሞ እንደሚለይ፣ጆሮም የንግግርን ለዛ ለይቶ ያውቃል።
4 የሚበጀንን እንምረጥ፣መልካሙንም አብረን እንወቅ።
5 “ኢዮብ እንዲህ ይላል፤ ‘እኔ ንጹሕ ነኝ፤እግዚአብሔር ግን ፍትሕ ነሣኝ፤
6 እውነተኛ ብሆንም፣እንደ ውሸታም ተቈጥሬአለሁ፤በደል ባይኖርብኝም፣በማይፈወስ ቍስል ተመትቻለሁ።’
7 ፌዝን እንደ ውሃ የሚጠጣት፣እንደ ኢዮብ ያለ ሰው ማን ነው?
8 ከክፉ አድራጊዎች ጋር ይተባበራል፤ከኀጢአተኞችም ጋር ግንባር ይፈጥራል።