42 የዳን ዘሮች በየጐሣቸው እነዚህ ነበሩ፤በስምዔ በኩል፣ የሰምዔያውያን ጐሣዎች።እነዚህ እንግዲህ የዳን ጐሣዎች ሲሆኑ፣
43 ሁሉም የሰምዔያውያን ጐሣዎች ነበሩ፤ ከእነዚህ የተቈጠሩት ደግሞ ሥልሳ አራት ሺህ አራት መቶ ነበሩ።
44 የአሴር ዘሮች በየጐሣቸው እነዚህ ነበሩ፤በዩምና በኩል፣ የዩምናውያን ጐሣ፣በየሱዋ በኩል፣ የየሱዋውያን ጐሣ፣በበሪዓ በኩል፣ የበሪዓውያን ጐሣ፤
45 እንዲሁም በበሪዓ ዘሮች በኩል፣በሔቤር በኩል፣ የሔቤራውያን ጐሣ፣በመልኪኤል በኩል፣ የመልኪኤላውያን ጐሣ።
46 አሴር ሤራሕ የምትባል ልጅ ነበረችው።
47 እነዚህ የአሴር ጐሣዎች ሲሆኑ፣ ከእነዚህ የተቈጠሩት አምሳ ሦስት ሺህ አራት መቶ ነበሩ።
48 የንፍታሌም ዘሮች በየጐሣቸው እነዚህ ነበሩ፤በያሕጽኤል በኩል፣ የያሕጽኤላውያን ጐሣ፣በጉኒ በኩል፣ የጉናውያን ጐሣ፣