17 “ምድሪቱን ርስት አድርገው የሚያከፋፍሏችሁ ካህኑ አልዓዛርና የነዌ ልጅ ኢያሱ ናቸው፤
18 ምድሪቱን በማከፋፈሉ እንዲረዱም ከየነገዱ አንዳንድ መሪ ውሰዱ።
19 ስማቸውም ይህ ነው፤ከይሁዳ ነገድ፣ የዮፎኒ ልጅ ካሌብ፤
20 ከስምዖን ነገድ፣የዓሚሁድ ልጅ ሰላሚኤል፤
21 ከብንያም ነገድ፣የኪስሎን ልጅ ኤልዳድ፤
22 የዳን ነገድ መሪ፣የዩግሊ ልጅ ቡቂ፤
23 የዮሴፍ ልጅ የምናሴ ነገድ መሪ፣የሱፊድ ልጅ አኒኤል፤