5 “የሞት ማዕበል ከበበኝ፤የጥፋትም ጐርፍ አሰጠመኝ።
6 የሲኦል ገመድ ተጠመጠመብኝ፤የሞትም ወጥመድ ተጋረጠብኝ።
7 በጨነቀኝ ጊዜ እግዚአብሔርን ጠራሁት፤ወደ አምላኬም ጮኽሁ።እርሱም ከመቅደሱ ድምፄን ሰማ፤ጩኸቴም ከጆሮው ደረሰ።
8 “ምድር ተንቀጠቀጠች፤ ተናወጠችም፤የሰማያትም መሠረቶች ተናጉ፤እርሱ ተቈጥቶአልና ራዱ።
9 ከአፍንጫው የቊጣ ጢስ ወጣ፤ከአፉ የሚባላ እሳት ነደደ፤ከውስጡም ፍሙ ጋለ።
10 ሰማያትን ሰንጥቆ ወረደ፤ከእግሩም በታች ጥቅጥቅ ያለ ደመና ነበረ።
11 በኪሩቤል ላይ ተቀምጦ በረረ፤በነፋስም ክንፍ መጠቀ።