ዘኁልቍ 23:5-11 NASV

5 እግዚአብሔርም (ያህዌ) በበለዓም አፍ መልእክት አስቀምጦ፣ “ወደ ባላቅ ተመልሰህ ይህን መልእክት ንገረው” አለው።

6 እርሱም ተመልሶ ሲሄድ ባላቅን ከመላው የሞዓብ አለቆች ጋር በመሠዊያው አጠገብ ቆሞ አገኘው።

7 ከዚያም በለዓም ንግሩን እንዲህ ሲል ጀመረ፤“ባላቅ ከአራም አመጣኝ፣የሞዓብ ንጉሥ ከምሥራቅ ተራሮች።‘ና ያዕቆብን ርገምልኝ፤መጥተህም እስራኤልን አውግዝልኝ’ አለኝ።

8 እግዚአብሔር (ኤሎሂም) ያልረገመውን፣እኔ እንዴት ረግማለሁ? እግዚአብሔር (ያህዌ) ያላወገዘውንስ፣እንዴት አወግዛለሁ?

9 ከዐለታማ ተራሮች ጫፍ ሆኜ አየዋለሁ፤በከፍታዎቹም ላይ ሆኜ እመለከተዋለሁ፤ተለይቶ የሚኖረውን፣ራሱንም ከሌሎች ሕዝቦች ጋር የማይቈጥረውን፣ ሕዝብ አያለሁ።

10 የያዕቆብን ትቢያ ማን ቈጥሮ ይዘልቃል?የእስራኤልንስ ሩብ ማን ይቈጥረዋል።የጻድቁን ሞት እኔ ልሙት፤ፍጻሜዬም የእርሱ ዐይነት ፍጻሜ ትሁን!”

11 ባላቅም በለዓምን፣ “እንዴት እንዲህ ታደርገኛለህ? ጠላቶቼን እንድትረግምልኝ አመጣሁህ፤ አንተ ግን ባረክሃቸው እንጂ ምንም አላደረግህልኝም!” አለው።