1 እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“ፍትሕን ጠብቁ፤መልካሙን አድርጉ፤ማዳኔ በቅርብ ነው፤ጽድቄም ፈጥኖ ይገለጣልና።
2 ሰንበትን ሳያረክስ የሚያከብር፣ክፉን ከማድረግ እጁን የሚሰበስብ፣ የሚገታ፣እነዚህን የሚፈጽም ሰው የተባረከ ነው።”
3 ወደ እግዚአብሔር የተጠጋ መጻተኛ፣“እግዚአብሔር በርግጥ ከሕዝቡ ይለየኛል” አይበል፤ጃንደረባም፣“እኔ ደረቅ ዛፍ ነኝ” አይበል።
4 እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“ሰንበቶቼን ለሚያከብሩ ጃንደረቦች፣ደስ የሚያሰኘኝን ለሚመርጡ፣ቃል ኪዳኔን፣ ለሚጠብቁ
5 በቤተ መቅደሴና በቅጥሮቼ ውስጥ፣ከወንዶችና ከሴቶች ልጆች የበለጠ፣መታሰቢያና ስም እሰጣቸዋለሁ፤ለዘላለም፣የማይጠፋ ስም እሰጣቸዋለሁ።
6 እርሱን ለማገልገል፣ራሳቸውን ከእግዚአብሔር ጋር ያቈራኙ መጻተኞች፣ የእግዚአብሔርን ስም በመውደድ፣እርሱንም በማምለክ፣ሰንበትን ሳያረክሱ የሚያከብሩትን ሁሉ፣ቃል ኪዳኔንም የሚጠብቁትን፣
7 ወደ ተቀደሰው ተራራዬ አመጣቸዋለሁ፤በጸሎት ቤቴም ውስጥ ደስ አሰኛቸዋለሁ።የሚቃጠል መሥዋዕታቸውንና ሌሎች መሥዋዕቶቻቸውን፣በመሠዊያዬ ቢሠዉ እቀበላቸዋለሁ፤ቤቴ፣ ለሕዝቦች ሁሉየጸሎት ቤት ተብሎ ይጠራልና።”