ኢሳይያስ

ምዕራፎች 5

መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም

ስለ ወይን ቦታ የተነገረ ቅኔ

1ስለ ወዳጄ፣ደግሞም ስለ ወይን ቦታው ልዘምር፤ወዳጄ በለምለም ኰረብታ ላይየወይን ቦታ ነበረው። 2መሬቱን ቈፈረ፤ ድንጋይንም ለቅሞ አወጣ፤ምርጥ የሆነውንም ወይን ተከለበት።በመካከሉ መጠበቂያ ማማ ሠራ፤የወይን መጭመቂያ ጒድጓድም አበጀ፤ከዚያ መልካም ፍሬ ያፈራል ብሎ አሰበ፤ነገር ግን ኮምጣጣ ፍሬ አፈራ። 3“እናንት በኢየሩሳሌም የምትኖሩና የይሁዳ ሰዎች ሆይ፤በእኔና በወይኔ ቦታ መካከል እስቲ ፍረዱ። 4ከዚህ ካደረግሁለት በላይ ለወይኔ ቦታ ምንሊደረግለት ይገባ ነበር?መልካም የወይን ፍሬ ያፈራል ብዬስጠብቅ ለምን ኮምጣጣ ፍሬ አፈራ? 5እንግዲህ በወይኔ ቦታምን እንደማደርግ ልንገራችሁ፤ዐጥሩን እነቅላለሁ፤ለጥፋት ይጋለጣል፤ግንቡንም አፈርሳለሁ፣መረጋገጫም ይሆናል። 6የማይኰተኰትና የማይታረምጠፍ መሬት አደርገዋለሁ፤ኵርንችትና እሾኽም ይበቅልበታል፤ዝናብም እንዳይዘንብበትደመናዎችን አዝዛለሁ።” 7የሰራዊት ጌታ የእግዚአብሔርየወይን ቦታው የእስራኤል ቤት ነው፤የይሁዳ ሰዎችምየደስታው አትክልት ናቸው።ፍትሕን ፈለገ፤ ነገር ግን ደም ማፍሰስን አየ፤ጽድቅን ፈለገ፤ ነገር ግን የጭንቅን ጩኸት ሰማ።

ወዮታና ፍርድ

8ስፍራ ለሌሎች እስከማይተርፍ፣ቤትን በቤት ላይ በመጨመር፣መሬትን ከመሬት ጋር በማያያዝ፣ለብቻችሁ በምድር ተስፋፍታችሁ ለምትኖሩ ወዮላችሁ 9የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ጆሮዬ እየሰማ እንዲህ ሲል ተናገረ፤“ታላላቅ ቤቶች ወና ይቀራሉ፣የሚያማምሩም ቤቶች ኗሪ ያጣሉ። 10ከሩብ ጋሻ የወይን ቦታ አንድ የባዶስ መስፈሪያ ያህል የወይን ጭማቂ ብቻ ይገኛል፤ አንድ የቆሮስ መስፈሪያ ዘር ተዘርቶ አንድ የኢፍ መስፈሪያ እህል ብቻ ይሰጣል። 11የሚያሰክር መጠጥ ፍለጋማልደው ለሚነሡ፣እስኪያነዳቸውም ወይን በመጠጣትሌሊቱን ለሚያነጉ ወዮላቸ 12በግብዣቸው ላይ በገናና መሰንቆ፣ከበሮና ዋሽንት እንዲሁም የወይን ጠጅ አለ፤ነገር ግን ለእግዚአብሔር ሥራ ቦታ አልሰጡም፤ለእጆቹም ሥራ ክብር አላሳዩም። 13ስለዚህ ሕዝቤዕውቀት በማጣቱ ይማረካል፤መኳንንቱም በራብ ይሞታሉ፤ሕዝቡም በውሃ ጥም ይቃጠላል። 14ስለዚህ ሲኦል ሆዷን አሰፋች፣አፏንም ያለ ልክ ከፈተች፤መኳንንቱና ሕዝቡ ከረብሸኞቻቸውና ከጨፋሪዎቻቸው ጋርወደዚያ ይወርዳሉ። 15ሰው ይዋረዳል፤የሰው ልጅም ዝቅ ዝቅ ይላል፤የእብሪተኛውም ዐይን ይሰበራል። 16የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ግን በፍትሕ ከፍ ከፍ ይላል፤ቅዱሱም አምላክ ቅድስናውን በጽድቅ ይገልጻል። 17በጎችም በገዛ መሰማሪያቸው እንደሚሰማሩ ሆነው ይግጣሉ፤የበግ ጠቦቶችም በባለጠጎች ፍርስራሽ ላይ ሣር ይበላሉ። 18ኀጢአትን በማታለል ገመድ ለሚስቡ፣በደልንም በሠረገላ ማሰሪያ ለሚጐትቱ ወዮላቸው! 19በዐይናችን እንድናይ እግዚአብሔር ይቸኵል፤ሥራውንም ያፋጥን፤የእስራኤልን ቅዱስ፣ የእርሱን ዕቅድእንድናውቃት ትቅረብ፤ትምጣም ለሚሉ ወዮላቸው!” 20ክፉውን መልካም፣መልካሙን ክፉ ለሚሉብርሃኑን ጨለማ፣ጨለማውን ብርሃን ለሚያደርጉ፣ጣፋጩን መራራ፣መራራውንም ጣፋጭ ለሚያደርጉ ወዮላቸው! 21ራሳቸውን እንደ ብልኅ ለሚቈጥሩ፣በራሳቸውም አመለካከት ጥበበኛ ለሆኑ ወዮላቸው! 22የወይን ጠጅ ለመጠጣት ጀግኖች፣የሚያሰክር መጠጥ ለመደባለቅ ብርቱ ለሆኑ ወዮላቸው! 23ጒቦን በመቀበል በደለኛን ንጹሕ ለሚያደርጉ፣ለበደል አልባ ሰው ፍትሕን ለሚነፍጉ ወዮላቸው! 24ስለዚህ የእሳት ነበልባል ገለባን እንደሚበላ፣ድርቆሽም በእሳት ጋይቶ እንደሚጠፋ፣የእነርሱም ሥር እንዲሁ ይበሰብሳል፤አበባቸውም እንደ ትቢያ ይበናል፤የሰራዊት ጌታ የእግዚአብሔርን ሕግ ንቀዋልና፤የእስራኤል ቅዱስ የተናገረውንም ቃል አቃለዋል። 25 የእግዚአብሔር ቍጣ በሕዝቡ ላይ ነዶአል፤እጁን አንሥቶ መቶአቸዋል፤ተራሮች ራዱ፤ሬሳዎችም በመንገድ ላይ እንደተጣለ ጥራጊ ሆኑ፤ይህ ሁሉ ሆኖ ግን ቍጣው ገና አልተመለሰም፤እጁም እንደ ተነሣ ነው። 26ከሩቅ ያሉትን ሕዝቦች የሚጠራበትንምልክት ያቆማል፤ከምድር ዳርቻም በፉጨት ይጠራቸዋል፤እነርሱም እየተጣደፉ በፍጥነት ይመጣሉ። 27በመካከላቸው ደካማና ስንኩል አይገኝም፤የሚያንቀላፋና የሚተኛ አይኖርም፤የወገባቸው መቀነት አይላላም፤የጫማቸውም ማሰሪያ አይበጠስም። 28ፍላጻቸው የተሳለ፣ቀስታቸውም የተደገነ ነው፤የሠረገሎቻቸውም መንኰራኵሮች እንደዐውሎ ነፋስ ናቸው። 29ጩኸታቸው እንደ አንበሳ ነው፤እንደ አንበሳ ደቦል ያገሣሉ፤ያደኑትንም ይዘው ይጮኻሉ፤ተሸክመውት ይሄዳሉ፤ የሚያስጥልም የለም። 30በዚያን ቀንእንደ ባሕር ሞገድ ይጮኹበታል፤ማንም ወደ ምድር ቢመለከት፣ጨለማንና መከራን ያያል፤ብርሃን እንኳ በደመናዎች ይጋረዳል።