ኢሳይያስ

ምዕራፎች 8

መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም

አሦር የእግዚአብሔር መሣሪያ

1 እግዚአብሔርም እንዲህ አለኝ፤ “ትልቅ ሰሌዳ ወስደህ፣ ‘ማኸር-ሻላል-ሃሽ-ባዝ’ ብለህ በተለመደው በሰው ፊደል ጻፍበት። 2እኔም፣ ካህኑን ኡሪያንንና የበራክዩን ልጅ ዘካርያስን ታማኝ ምስክሮቼ እንዲሆኑ እጠራቸዋለሁ።” 3እኔም ወደ ነቢዪቱ ሄድሁ፤ እርሷም ፀነሰች፤ ወንድ ልጅም ወለደች። እግዚአብሔርም፣ እንዲህ አለኝ፤ “ስሙን ማኸር-ሻላል-ሃሽ-ባዝ ብለህ ጥራው። 4ሕፃኑም፣ ‘አባባ’ ወይም ‘እማማ’ ብሎ መጥራት ከመቻሉ በፊት፣ የደማስቆ ሀብትና የሰማርያ ምርኮ በአሦር ንጉሥ ይወሰዳል።” 5 እግዚአብሔርም እንደ ገና እንዲህ ሲል ተናገረኝ፤ 6“ይህ ሕዝብ በጸጥታ የሚፈሰውንየሰሊሆምን ውሆች ትቶ፣በረአሶንናበሮሜልዩ ልጅ ተደስቶአልና። 7ስለዚህ ጌታ ታላቁንና ብርቱውንየጐርፍ ውሃ፣የአሦርን ንጉሥ ከነግርማ ሞገሱ ሁሉ ያመጣባቸዋል።ውሃውም ከቦዩ ዐልፎ ተርፎበወንዙ ዳር ያለውን ምድር ሁሉ ያጥለቀልቃል፤ 8እየጠራረገ ወደ ይሁዳ ይወርዳል፤እያጥለቀለቀ ያልፋል፤እስከ ዐንገትም ይደርሳል፤አማኑኤል ሆይ፤የተዘረጉ ክንፎቹ ምድርህን ከዳር እስከዳር ይሸፍናሉ።” 9እናንተ አሕዛብ፣ ፎክሩ፤ግን ደንግጡ።በሩቅ አገር ያላችሁ አድምጡ፤ለጦርነትም ተዘጋጁ፤ ነገር ግን ደንግጡ፤ለጦርነትም ተዘጋጁ፤ ነገር ግን ደንግጡ፤ 10ተመካከሩ፤ ግን አይሳካም፤ዕቅድ አውጡ፤ ሆኖም አይጸናም፤እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ነውና።

እግዚአብሔርን ፍሩ

11 እግዚአብሔር ብርቱ እጁን በላዬ አድርጎ የእነዚህን ሰዎች መንገድ እንዳልከተል አስጠነቀቀኝ፤ እንዲህም አለኝ፤ 12“እነዚህ ሰዎች፣ ‘አድማ’ ብለው የሚጠሩትን፣ማንኛውንም ነገር፣ ‘አድማ’ አትበሉ፤እነርሱ የሚፈሩትን አትፍሩ፤አትሸበሩለትም። 13ልትቀድሱ የሚገባው የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔርን ብቻ ነው፤ልትፈሩት የሚገባው እርሱን ነው፤ልትንቀጠቀጡለት የሚገባውም እርሱ ነው። 14እርሱም መቅደስ ይሆናል፤ለሁለቱ የእስራኤል ቤት ግንየሚያደናቅፍ ድንጋይየሚያሰናክልም ዐለት ይሆንባቸዋል፤ለኢየሩሳሌም ሕዝብምወጥመድና አሽክላ ይሆናል። 15ከእነርሱ ብዙዎች ይሰናከላሉ፤ይወድቃሉ፤ ይሰበራሉ፤ወጥመድ ይገባሉ፤ ይያዛሉም።” 16ምስክርነቱን አሽገው፤ሕጉንም በደቀ መዛሙርቴ መካከል አትመው። 17ፊቱን ከያዕቆብ ቤት የሸሸገውን እግዚአብሔርን እጠብቃለሁ፤እርሱንም ተስፋ አደርጋለሁ። 18እነሆ፤ እኔና እግዚአብሔር የሰጠኝ ልጆች በጽዮን ተራራ ከሚኖረው ከሰራዊት ጌታ ከእግዚአብሔር ለእስራኤል ምልክትና ድንቅ ነን። 19ሰዎች፣ “የሚያነበንቡትንና የሚያሾካ ሹኩትን ሟርተኞችንና መናፍስት ጠሪዎችን ጠይቁ ቢሏችሁ፣ ሕዝቡ አምላኩን መጠየቅ አይገባውምን? በሕያዋን ምትክ ሙታንን መጠየቅ ለምን አስፈለገ? 20ወደ ሕጉና ወደ ምስክር ቃሉ ሂዱ! እነርሱም እንዲህ ያለውን ቃል ባይናገሩ የንጋት ብርሃን አይበራላቸውም። 21ተጨንቀውና ተርበው በምድሪቱ ላይ ይንከራተታሉ፤ ክፉኛ ሲራቡም ይቈጣሉ፤ ወደ ላይ እየተመለከቱ ንጉሣቸውንና አምላካቸውን ይራገማሉ። 22ከዚያም ወደ ምድር ይመለከታሉ፣ የሚያዩትም ጭንቀት፣ ጨለማና የሚያስፈራም ጭጋግ ብቻ ነው፤ ወደ ድቅድቅ ጨለማም ይጣላሉ።