4 እንዲህም በለው፤ ‘ተጠንቀቅ፤ ተረጋጋ፤ አትፍራ በእነዚህ ከእሳት ተርፈው በሚጤሱት በሁለቱ የዕንጨት ጒማጆች፣ በሶርያና በንጉሥዋ በረአሶን እንዲሁም በሮሜልዩ ልጅ ቍጣ አትሸበር።
5 ሶርያ ኤፍሬምና፣ የሮሜልዩ ልጅ ሊያጠፉህ እንዲህ ብለው ተማከሩ፤
6 “ይሁዳን እንውረር፤ እንበታትነው ተከፋፍለንም እንግዛው፤ የጣብኤልንም ልጅ እናንግሥባት።”
7 ልዑል እግዚአብሔር ግን እንዲህ ይላል፦“ ‘ይህ ምክራቸው አይፈጸምም፤ከቶም አይደረግም፤
8 የሶርያ ራስ ደማስቆ፣የደማስቆ ራስ ረአሶን ነውና፤በሥልሳ አምስት ዓመት ውስጥ፣የኤፍሬም ሕዝብ ይበታተናል፤ ሕዝብመሆኑም ይቀራል።
9 የኤፍሬም ራስ ሰማርያ፣የሰማርያም ራስ የሮሜልዩ ልጅ ነው።እንግዲህ በእምነታችሁ ካልጸናችሁ፣ፈጽሞ መቆም አትችሉም።’ ”
10 እንደ ገናም እግዚአብሔር አካዝን እንዲህ አለው፤