ኢሳይያስ 8:7-13 NASV

7 ስለዚህ ጌታ ታላቁንና ብርቱውንየጐርፍ ውሃ፣የአሦርን ንጉሥ ከነግርማ ሞገሱ ሁሉ ያመጣባቸዋል።ውሃውም ከቦዩ ዐልፎ ተርፎበወንዙ ዳር ያለውን ምድር ሁሉ ያጥለቀልቃል፤

8 እየጠራረገ ወደ ይሁዳ ይወርዳል፤እያጥለቀለቀ ያልፋል፤እስከ ዐንገትም ይደርሳል፤አማኑኤል ሆይ፤የተዘረጉ ክንፎቹ ምድርህን ከዳር እስከዳር ይሸፍናሉ።”

9 እናንተ አሕዛብ፣ ፎክሩ፤ግን ደንግጡ።በሩቅ አገር ያላችሁ አድምጡ፤ለጦርነትም ተዘጋጁ፤ ነገር ግን ደንግጡ፤ለጦርነትም ተዘጋጁ፤ ነገር ግን ደንግጡ፤

10 ተመካከሩ፤ ግን አይሳካም፤ዕቅድ አውጡ፤ ሆኖም አይጸናም፤እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ነውና።

11 እግዚአብሔር ብርቱ እጁን በላዬ አድርጎ የእነዚህን ሰዎች መንገድ እንዳልከተል አስጠነቀቀኝ፤ እንዲህም አለኝ፤

12 “እነዚህ ሰዎች፣ ‘አድማ’ ብለው የሚጠሩትን፣ማንኛውንም ነገር፣ ‘አድማ’ አትበሉ፤እነርሱ የሚፈሩትን አትፍሩ፤አትሸበሩለትም።

13 ልትቀድሱ የሚገባው የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔርን ብቻ ነው፤ልትፈሩት የሚገባው እርሱን ነው፤ልትንቀጠቀጡለት የሚገባውም እርሱ ነው።