7 ምድራቸው በብርና በወርቅ ተሞልታለች፤ሀብታቸውም ልክ የለውም።ምድራቸው በፈረሶች ተሞልታለች፤የሠረገሎቻቸውም ብዛት ልክ የለውም።
8 ምድራቸው በጣዖታት ተሞልታለች፤ጣቶቻቸው ላበጇቸው፣ለእጆቻቸው ሥራ ይሰግዳሉ።
9 ሰው ዝቅ ብሎአል፤የሰው ልጅም ተዋርዶአል፤ስለዚህ በደላቸውን ይቅር አትበል።
10 ከእግዚአብሔር አስፈሪነት ከግርማው ሽሽ፤ወደ ዐለቶች ሂድ፤በመሬትም ውስጥ ተሸሸግ።
11 የእብሪተኛ ሰው ዐይን ይሰበራል፤የሰዎችም ትዕቢት ይዋረዳል፤በዚያን ቀን እግዚአብሔር ብቻውን ከፍ ከፍ ይላል።
12 የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔርእብሪተኛውንና ትዕቢተኛውን ሁሉ፣የተኵራራውን በሙሉየሚያዋርድበት ቀን አለው።
13 ረዥምና ከፍ ከፍ ያሉትን የሊባኖስ ዝግባዎች ሁሉ፣የባሳንን የወርካ ዛፎች ሁሉ፣