ኢሳይያስ 25:2-8 NASV

2 ከተማዪቱን የድንጋይ ክምር አድርገሃታል፤የተመሸገችውንም ከተማ አፈራርሰሃታል፤የተመሸገችው የባዕድ ከተማ ከእንግዲህ አትኖርም፤ተመልሳም አትሠራም።

3 ስለዚህ ብርቱ ሕዝቦች ያከብሩሃል፤የጨካኝ አሕዛብ ከተሞችም ይፈሩሃል።

4 ለድኻ መጠጊያ፣በጭንቅ ጊዜ ለችግረኛ መጠለያ፣ከማዕበል መሸሸጊያ፣ከፀሓይ ትኵሳትም ጥላ ሆነሃል።የጨካኞች እስትንፋስ፣ከግድግዳ ጋር እንደሚላጋ ማዕበል ነውና፤

5 እንደ ምድረ በዳም ትኵሳት ነው።የባዕድን ጩኸት እረጭ ታደርጋለህ፤ትኵሳት በደመና ጥላ እንደሚበርድ፣የጨካኞችም ዝማሬም እንዲሁ ጸጥ ይላል።

6 የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር በዚህ ተራራ ላይ፣ለሕዝብ ሁሉ ታላቅ የምግብ ግብዣ፣የበሰለ የወይን ጠጅ ድግስ፣ማለፊያ ጮማና ምርጥ የወይን ጠጅ ያዘጋጃል።

7 በዚህም ተራራ ላይ፣በሕዝብ ሁሉ ላይ የተጣለውን መጋረጃ፣በመንግሥታት ላይ የተዘረጋውን መሸፈኛ ያጠፋል፤

8 ሞትንም ለዘላለም ይውጣል።ጌታ እግዚአብሔርከፊት ሁሉ እንባን ያብሳል፤የሕዝቡንም ውርደትከምድር ሁሉ ያስወግዳል፤ እግዚአብሔር ተናግሮአልና።