5 እግዚአብሔር በአርያም ተቀምጦአልና ከፍ ከፍ አለ፤ጽዮንን በጽድቅና በፍትሕ ይሞላታል።
6 እርሱ ለዘመንህ የሚያስተማምን መሠረት፣የድነት፣ የዕውቀትና የጥበብ መዝገብ ይሆናል፤ እግዚአብሔርንም መፍራት የዚህ ሀብት ቍልፍ ነው።
7 እነሆ፤ ጐበዞቻቸው በየመንገዱ ይጮኻሉ፤የሰላም መልእክተኞችም አምርረው ያለቅሳሉ።
8 አውራ ጐዳናዎች ባዶ ናቸው፤በመንገድ ላይ ሰው የለም፤ስምምነቱ ፈርሶአል፤መካሪዎቹ ተንቀዋል፤የሚከበርም የለም።
9 ምድሪቱ አለቀሰች፤ መነመነች፤ሊባኖስ ዐፈረች፤ ጠወለገች፤ሳሮን እንደ ዐረባ ምድረ በዳ ሆነች፤ባሳንና ቀርሜሎስ ቅጠላቸውን አረገፉ።
10 እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ “አሁን እነሣለሁ፤አሁን ከፍ ከፍ እላለሁ፤አሁን እከብራለሁ።
11 ገለባን ፀነሳችሁ፤እብቅንም ወለዳችሁ፤እስትንፋሳችሁም የሚበላችሁ እሳት ነው።