3 “እናንት በኢየሩሳሌም የምትኖሩና የይሁዳ ሰዎች ሆይ፤በእኔና በወይኔ ቦታ መካከል እስቲ ፍረዱ።
4 ከዚህ ካደረግሁለት በላይ ለወይኔ ቦታ ምንሊደረግለት ይገባ ነበር?መልካም የወይን ፍሬ ያፈራል ብዬስጠብቅ ለምን ኮምጣጣ ፍሬ አፈራ?
5 እንግዲህ በወይኔ ቦታምን እንደማደርግ ልንገራችሁ፤ዐጥሩን እነቅላለሁ፤ለጥፋት ይጋለጣል፤ግንቡንም አፈርሳለሁ፣መረጋገጫም ይሆናል።
6 የማይኰተኰትና የማይታረምጠፍ መሬት አደርገዋለሁ፤ኵርንችትና እሾኽም ይበቅልበታል፤ዝናብም እንዳይዘንብበትደመናዎችን አዝዛለሁ።”
7 የሰራዊት ጌታ የእግዚአብሔርየወይን ቦታው የእስራኤል ቤት ነው፤የይሁዳ ሰዎችምየደስታው አትክልት ናቸው።ፍትሕን ፈለገ፤ ነገር ግን ደም ማፍሰስን አየ፤ጽድቅን ፈለገ፤ ነገር ግን የጭንቅን ጩኸት ሰማ።
8 ስፍራ ለሌሎች እስከማይተርፍ፣ቤትን በቤት ላይ በመጨመር፣መሬትን ከመሬት ጋር በማያያዝ፣ለብቻችሁ በምድር ተስፋፍታችሁ ለምትኖሩ ወዮላችሁ
9 የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ጆሮዬ እየሰማ እንዲህ ሲል ተናገረ፤“ታላላቅ ቤቶች ወና ይቀራሉ፣የሚያማምሩም ቤቶች ኗሪ ያጣሉ።